ወደ አለም መጥፋት ተቃርበናል? በአሁኑ ወቅት ሀገሮች በጦርነት፣ በሽታ፣ እሳት፣ አውሎ ንፋስ እና በመሬት መንቀጥቀጥ እየጠፉ ነው፡፡ ሰይጣን ሁል ጊዜ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር በሌላ ባህሪ ይቀይራል፡፡ በክርስቶስና በሰይጣን ያለው ታላቁ ግጭት በአለም ታሪክ ሁሉ ታይቷል፡፡ በቅርቡም ፕላኔታችን በከፍተኛ ችግርን የተሞሉ ክስተቶች ብትጠቃም ኢየሱስ እንደሚመለስ ቃል በመግባት እርሱን የሚያምኑትን ከሞት በማዳን ሀጢያትን ለዘላለሙ ያጠፋል፡፡